Showing posts with label የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ. Show all posts
Showing posts with label የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ. Show all posts

Tuesday, September 29, 2009

የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ

የሚገርመው ነገር «መልከ ጥፉን በስም ይደግፉ» እንዲሉ እነዚህ እራሳቸውን ማህበረ ቅዱሳን እያሉ የሚጠሩ ማህበረ ሰይጣኖች በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ስር ነን እያሉ እንደ መዥገር ተለጥፈው ንጹሐን ወንድሞችንና እህቶችን በማሳሳት አባቶችን እንዲሳደቡ የሚያደርጉ አንዴ በቅዱሳን ስም እራሳቸውን ማህበረ ቅዱሳን ደግሞም የጥፋት መልእክተኞች እንደሆኑ እያወቅናቸው እራሳቸውን በሌላ ስም ደጀ ሰላም ብለው አሁንም የማጭበርበር ሥራቸውን እንደ ቀጠሉ አሉ። እኔን የሚያሳዝነኝ ግን እነሱ ለነፍሳቸው የማይራሩ መሆናቸውና እንደ ድሮው ባይሆንም አሁንም ድረስ በነዚህ ማህበረ ሰይጣኖች የሚታለሉት ወንድሞችና እህቶች ናቸው።


«አውቆ የተኛን ቢቀሰቅሱት አይነቃም» እንዲሉ ለማህበሩ መሪዎች ነን ለሚሉት በመምከር ጊዜዬን አላጠፋም። በፍጹም ልባቸው እግዚአብሔርን ብለው ይቅርታ ለማግኘትና ላደረገላቸው ነገር ምስጋና ለማቅረብ ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለሚመጡ በደመ ክርስቶስ የከበሩ ንጹሐን ወንድሞችና እህቶች ግን አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ጠቅሼ ለማለፍ እወዳለሁ፥


«የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሩአችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፥ የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው። ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ እስከ ለዘላለምም ያው ነው።» ወደ ዕብራውያን 1378


ቅዱስ ቃሉ «ዋኖቻችሁን» የሚለው ሰላም ለኪ ሳይሉና ሀብተ ክህነት ሳይኖራቸው በራሳቸው ፈቃድ በቅዱሳን ስም ማህበር አቋቁመው አስራት የሚሰበስቡትን ሳይሆን በነ ቅዱስ ጴጥሮስ ወንበር የተተኩትን ቅዱሳን አባቶችን እንደሆነ ይህን እውነት መገንዘብ የሚያስቸግራችሁ አይመስለኝም። እባካችሁ የነፍሳችሁ ቤዛ ወደሆነው ወደጌታችንና ወደመድኃኒታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ተመልከቱ። እግዚአብሔር አምላክ በቅዱስ ልጁ የጠራን ለአመጻ ሳይሆን ለመዳንና ብሎም ለኛ ያዘጋጀልንን ሰማያዊ ቤት ለማውረስ ነው። ይህ ደግሞ በአመጻ፣ አበውን በመሳደብና በማዋረድ የሚገኝ አይደለም። እባካችሁ እናስተውል። ቤተ ክርስቲያን አንዲት ናት የመናፍቅና የኢአማንያን ሳይበቃ እኛ ገና ለእምነቱ ሕጻናት የሆነው ለአባቶች ህመም አንሁንባቸው። ሁሉን ትታችሁ አበውን ጠይቁ ንጹሁን እምነታችንን ያስተምሩዋችኋል። እራሳቸውን ለዚህ ቅዱስ አገልግሎት አሳልፈው የሰጡ ቅዱሳን አባቶች በክርስቶስ ፍቅርና ትህትና ያስተምሩናል። የኑሮአቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታቸው ምሰሉአቸው። የእግዚአብሔርን ስም እየጠሩ በግብራቸው የካዱትን ሳይሆን በኑሮአቸው የሚመስሉትን ምሰሉ።